Friday, May 17, 2013

ዶላር ከዜጎቹ የበለጠበት ኢህአዴግ


mittal metho

ስለ መሬት ነጠቃው ኢህአዴግ “እንወያይ” አለ

“መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ  ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር።
“ትግል አርቆ ማሰብ ይጠይቃል፤ እቅድ ይፈልጋል። ትግል ህዝብን ማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልምና ራዕይ ሊኖረው ያስፈልጋል። ስለዚህ ምን እናድርግ? ከየት እንጀምር?” የሚል ጥያቄ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች አነሱ። አቶ ኦባንግም የሚመሩት ድርጅት ዕቅዱና ራዕዩ በሂደት እዚህ እንዳደረሰው አስረዱ። በቀጣይም ከህንድ ዜጎች ስለሚጠበቀው ዋንኛ ትግል አወሱ። ካሩቱሪ የሚባለው ኩባንያ በኢንቨስትመንት ስም እያከናወነ ያለውን ተግባር ህንዶች ካሳለፉት የቀደመው ችግራቸው ጋር በማያያዝ ተናገሩ። መሃትማ ጋንዲ ገድል ፈጽመው ያለፉበትን ትግል በማድመቅ ይህ ትውልድ የጋንዲን ዓላማ በማንሳት ለወገኖቹ ስቃይ የመድረስ ግዴታና የታሪክ ውርስ እንዳለበት አሳሰቡ። በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ በመረጃ ተንትነው አብራሩ።
ኦባንግ “ጥቁሩ ሰው” ወደ ህንድ ያመሩት ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር ለመነጋገር አልነበረም። በመጀመሪያ የተገኙት የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል “Understanding Land Investment in East Africa” በሚል ስያሜ ባዘጋጀው ምክከርና የትግል ልምድ መለዋወጫ መድረክ ላይ ንግግር እንዲያቀርቡ ተጋብዘው ነው። አስቀድሞ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲሳተፉ በጋራ ንቅናቄው የተመረጡ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ግለሰቦች የነበሩ ቢሆንም ከወጪ እና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶቹ ካጋጠማቸው ሌሎች ተዛማች ችግሮች ምክንያት ሳይሳካ እንደቀረ ተጠቅሷል፡፡
በዚሁ ታላቅ መድረክ ላይ ኦባንግ “ነጻ ስለመሆን የማንንም ፈቃድ አንጠይቅም። ሰው በሰውነቱ የሚከበርበት አገር እስከምንመሰርት ድረስ እንታገላለን። የብሶታችንና የትግላችን መነሻ ለናንተ አዲስ ትግል አይደለም” በማለት የስብሰባውን ቀልብ አነሱት። በህንድ የነጻነት ትግል ውስጥ አብሪ ኮከብ ሆነው የሚኖሩትን መሃትማ ጋንዲን በማስታወስ አገራቸውን ተቀራምተው የነበሩትን የእንግሊዝ የመሬት ቀማኞች እንዴት ድል እንደመቱ አሞካሽተው አቀረቡ። ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጥያቄ መልስ የሰጡት አቶ ኦባንግ በዩኒቨርስቲው ንግግራቸው ጋንዲን ማጉላታቸው ብቻ ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ውስጥ ሌሎች ጋንዲዎች ስለመኖራቸው መናገራቸው ታላቅ ትርጉም የሰጠ እንደነበር ገልጸዋል።
በምክክሩ ላይ የክብር ተናጋሪ የነበሩት የኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር አኑራድሃ ሚታል “በኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ሁሉ በፍጹም ተቀባይነት የለውም” በማለት ምክንያታቸውን አስረዱ። በኢትዮጵያ በወልቃይት ጠገዴ፣ በዋልድባ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ ስለተካሄደው መሬት ንጥቂያና ግፍ የተሞላበት ተግባር በዝርዝር አቀረቡ። የአኑራድሃ ንግግር ህንዶቹን አስደነገጠ።
የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል ባዘጋጀው በዚህ የምክክርና የትግል ስልት የልውውጥ መድረክ የህንድ ፖለቲከኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋንዲያዊ የትግል መስመር አጥብቀው የሚከተሉ የተለያዩ ፖለቲከኞች፣ የህንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ የገዢው ፓርቲ ተወካዮች፣ የቀድሞ ፖለቲከኞች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ተሟጋቾች፣ ተለያዩ ማህበራት ተወካዮችና የተለያዩ አካላት የተገኙ ሲሆን ታላላቅ የመገናኛ አውታሮችም ተገኝተዋል።
ዶላር ከዜጎቹ የበለጠበት ኢህአዴግ
“ህወሃት/ኢህአዴግ ዶላር ካገኘ ለሚገባበት ገደል የሚቀርበውን አፋፍ አይመርጥም” በማለት የሚተችበትን ነጥብ ማስታወስ አግባብ ይሆናል። ኢህአዴግ ከስልጣኔ፣ ከወገኖቻቸውና ከዓለም መገናኛ ጀርባ ያሉ፣ በመረጃ ጨለማ ውስጥ የሚኖሩ ምስኪን ዜጎችን በሚዘገንን የንዋይ ፍቅር መብታቸውን እየጨፈለቀ ለመናገር የሚታክት በደል ፈጽሞባቸዋል። አኑራድሃ እንዳሉት “መሬት የመንግስት ነው” በሚል ዜጎችን የግድግዳና ጣሪያ ባለቤት በማድረግ ከቅድመ አያት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ሃብታቸውን ዘርፏቸዋል።
ይህ አገር እየመራ እንኳን ራሱን በነጻ አውጪ ስም የሚጠራ ድርጅት በር ዘግቶ በዜጎቹ ላይ የሚፈጽመውን ተግባር በማጋለጥ ቅድሚያ የያዘው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ነበር። ይህንን አቢይ ተግባር ጊዜ በመውሰድ ያጠናውና በመረጃ በማስደገፍ ስርዓቱ የህዝቦችን ደም እንደሚጠጣ ያጋለጠው አቶ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ለነዚህ ወገኖች አንደበት በመሆን በዝግ የሚፈጸመውን ርህራሄ የጎደለው ግፍ ይፋ እንዲሆን አደረገ። “እመራዋለሁ” የሚለውን ህዝብ በንዋይ፣ ለዚያውም በዓለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሂሳብ ድንግል መሬት የሚቸበችበው ህወሓት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ አንድ ሄክታር መሬት ከአንድ ዶላር በታች እንደ ጉሊት ጨው መቸርቸሩ ይፋ መሆኑንን ከሰሙ መካከል የኦክላንድ ተቋም ቀዳሚ ሆነ።
በቅርቡ የአማርኛው ትርጉም ይፋ የሚሆነውን “በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” የተሰኘውን ጥናት ያካሄደው የኦክላንድ ተቋም አቶ ኦባንግ ከሚመሩት ድርጅት ጋር በጋራ እየሰራ የሚገኝ ነው፡፡ ይህንንም ጥናት ተግባራዊ ለማድረግና በዘገባ መልክ ለማውጣት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያደረገውን አስተዋጽዖ የተቋሙ ዳይሬክተር በአደባባይ የሚመሰክሩት ሲሆን ለጥናቱ የጀርባ አጥንት በመሆን ያሳየውን ዕገዛ ያደንቃሉ፡፡ ተቋማቸው ባደረገው በዚህ ጥናት ኢትዮጵያን አስተዳድራለሁ የሚለው ኢህአዴግ ዜጎቹን ሳያማክርና ፈቃድ ሳይጠይቅ እንደ አሮጌ እቃ በየስርቻው የሚጥል አገዛዝ መሆኑን በማስረጃና በተግባር አራግፈው በአደባባይ ሰቀሉት።
ህንድ እንዴት ተደረሰ?
“የወረቀት ትግል ውጤት የለውም” ሲሉ የሚከራከሩ ነበሩ። አሁንም አሉ። አቶ ኦባንግ ግን በተቃራኒው ይህንን አስተሳሰብ አይቀበሉም። ህንድ አገር ስለመድረሳቸው ዋና ምክንያትና አጋጣሚ ተጠይቀው “ህንድ አገር ባጋጣሚ አልሄድኩም” በማለት መልሳቸውን ይጀምራሉ። በኢትዮጵያ ያለውን ስርዓት የለቀቀ አገዛዝ የሰለቻቸውን ዜጎች ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት ድርጅታቸው በየደረጃው ያስቀመጣቸው አካሄዶች እንዳሉ ይናገራሉ። “ህንድ አገር በመሄድ የህዝብ ለህዝብ የተቀናጀ ትግል እንደምናደርግ ያቀድነው አስቀድመን ነው። በዚህ አያቆምም። በእቅዳችን መሰረት እንቀጥላለን” የሚሉት ኦባንግ ሜቶ በኢትዮጵያ የሚካሄደው የመሬት ዝርፊያ ማቆሚያ እንደሚበጅለት በርግጠኛነት ያስረዳሉ። ይህ ግን የድርጅታቸው የመጨረሻ ግብ አይደለም።
ምን ውጤት ተገኘ?
ካሩቱሪ የተባለው ድርጅት በኢትዮጵያ ድንግል መሬት በመውሰድ ቅድሚያ አለው። ይህ ድርጅት የሚጠራው በህንዶች ስም ነው። በህንድ መንግስት በተወሰነ መልኩ የሚደገፍም ነው። በርካታ የአክሲዮን ባለድርሻዎችን ያሰባሰበ ነው። መሰረታዊው የምክክሩ ዓለማ የህንድ ወንድምና እህት ህዝብ እያወቁ እነሱ ታግለው ድል የነሱት የመሬት ዝርፊያ በነሱ ስም በሃያ አንደኛው ክፍለዘመን በኢትዮጵያዊያን ላይ መካሄዱን ማሳወቅ ነበር።
በዚሁ መሰረት ዜጎች ከራሳቸው ምድር ላይ እየተፈናቀሉ፣ እየተገረፉ፣ እየተገደሉ፣ እየተሰደዱ ወዘተ መከራ ሲደርስባቸው እንደነበር የሰሙ አዘኑ። “ይህ በስማችን ስለመደረጉ አናውቅም ነበር” ሲሉ ሃዘናቸውን ገለጹ። አንድ አዛውንት የስብሰባው ተሳታፊ “በኢትዮጵያና በህንድ ህዝብ መካከል ልዩነት የለም። አንድ ነን። ተያይዘን እንታገላለን። ህብረት እንፈጥራለን። ተያይዘን የምንታገልበት አንድ ቀን አሁን ነው” ሲሉ አስተያየት ሰጡ።
“ትግል እቅድ ይጠይቃል። ትግል ህዝብን የማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልም ሊኖረው ይገባል። አሁን ምን እናድርግ? ከምን እንጀምር” የሚል ጥያቄና የትግል ዝግጁነት ተሰማ። ለተከታታይ ቀናት የተካሄደውን ምክክር የህንድ ብሄራዊ ሚዲያዎችና ታዋቂ የዓለም መገናኛዎች ለህብረተሰቡ ይመግቡ ስለነበር፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ውይይት በመደረጉ ካሩቱሪ ተሸበረ።
የህንድ ዜጎች ምን ያደርጋሉ?
“በስማችን ወንጀል ሊሰራ አይገባም። በመንግስት ስም የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲካሄድ ዝም ብለን አንመለከትም። መንግስት ለካሩቱሪየሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ እንዲያቆም፣ የካሩቱሪ ባለ አክሲዮኖች ለዚህ ክፉ ተግባር ተባባሪ ከመሆን ተቆጠቡ” የሚሉና በየደረጃው እየጠነከረ የሚሄድ ማስገደጃ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተሳታፊዎቹ አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ባለሃብቱንና ባለ አክሲዮኖቹን በማስጨነቁ የድርጅቱ የባለ አክሲዮኖች ስብሰባ ከመካሄዱ በፊት የሚጀመረው ዘመቻ በጎርፍና በከብት መንጋ ኪሳራ ደርሶበት የነበረውን ኩባንያ በኪሳራ እስከማዘጋት የሚደርስ ትግል እንደሚደረግ ቃል ከማስገባት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ አቶ ኦባንግ ይናገራሉ። አይያዘውም “የሰከነ ትግል ውጤቱ አሁንም በሰከነ መንፈስ በመከታተል የሚታይ ይሆናል። በዚህ አይበቃም ይቀጥላል። በስሜትና ጊዜያዊ በሆኑ ጥቅሞች ሳንነዳ እቅዳችንና ግባችን በሚያዘን መሰረት እንጓዛለን” ሲሉ ለጎልጉል ተናግረዋል።
መንግስት ለምን ፈራ?
ኢህአዴግ ስብሰባውንና የስብሰባውን ውጤት የፈራው ጥቅሙን ስለሚያጣ ነው። ካሩቱሪ ለቅቆ ሲወጣ ሁሉም መሬት ለመንጠቅ የመጡ ባለሃብቶች በየተራ ይወጣሉ። ይህ ዶላር ፍለጋ የሚምልባቸውን ምስኪን ህዝቦች እየገፋ ያለ ስርዓት ለአፈናው ለሚያወጣው ከፍተኛ በጀት፣ ለተነከረበት ከፍተኛ ሙስናና ዝርፊያ የሚሆን ገቢ ሲያንሰው የራሱ “ሌቦች” ጭምር ስለሚከዱት የህንድ ወገኖች እያሳዩ ያሉት ተቃውሞ ሳይነድና ሳይጠነክር አስቀድሞ ለማስቆም ህወሃት/ኢህአዴግ ሩጫ ጀምሯል።
የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት በህንድ አገር የተካሄደው ምክክር በተጠናቀቀበት እለት ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ለኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ደብዳቤ ተጽፎላቸዋል። ደብዳቤው ዋና ዳይሬክተሯን ለማነጋገር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ጉዳዩም አሁን በተጀመረው ዘመቻ ዙሪያ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። አቶ ኦባንግ ጉዳዩን አስመልክቶ ለተጠየቁት ሲመልሱ “የመሬት ነጠቃን በተመለከተ ማንኛውም ዓይነት ውይይት አይታሰብም። የተላከው ደብዳቤ ምንም ይሁን ምን አኑራድሃ ስለ ኢትዮጵያ መንግስትና ስለ ቅጥፈቱ ከበቂ በላይ መረጃ ስላላቸው ሊያሳስቷቸው አይችሉም። እኛም በብዙ ፈርጁ ከምናካሂደው ትግል አንዱ በመሆኑ ነቅተን ጉዳዩን እንከታተለዋለን” የሚል መልስ ሰጥተዋል

Thursday, May 16, 2013

በባለሥልጣናትና በባለሀብቶች ላይ ምርመራው የተጀመረው በቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መመርያ መሆኑ ተገለጸ


 

ሪፖርተር
15 may 2013
-ፀረ ሙስና ኮሚሽን በዕርምጃው መዘግየት ተጠይቋል


-ኮሚሽነሩ ያለመከሰስ መብት ያለው የለም አሉ
ባለፈው ዓርብ በፌደራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ተጠርጥረው በተያዙት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣናት፣ ባለሀብቶችና ትራንዚተሮች ጉዳይ ላይ ማክሰኞ ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ እንዲሰጡ የተጠየቁት ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ወቅት በሰጡት የሥራ መመርያ መሠረት ጥናት ተደርጐ የተከናወነ መሆኑን አስታወቁ፡፡
ኮሚሽነሩ የመሥሪያ ቤታቸውን የአሥር ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ግንቦት 6 ቀን 2005 ዓ.ም. ረፋዱ ላይ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከማቅረባቸውም በተጨማሪ፣ በዚሁ ቀን ከሰዓት በኋላ በዚሁ ጉዳይ ላይ ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ከፓርላማ አባላት ባለፈው ሳምንት በተያዙት ባለሥልጣናት፣ ባለሀብቶችና ሌሎች ላይ ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡
ኮሚሽኑን የሚከታተለው ምክር ቤት የሕግና አስተዳደር ቋሚ ኮሚቴ በጉዳዩ ላይ ከሕዝብ የሰበሰባቸው ጥያቄዎች ዋነኞቹ ነበሩ፡፡ «ዕርምጃው ቆራጥነትን የተሞላበት ቢሆንም ሕዝቡ አምርሮና አልቅሶ በመንግሥት ላይ ጥርጣሬ ካደረበት በኋላ ነው የተወሰደው፡፡ ለምን ይህን ያህል ጊዜ ዘገየ?» የሚል ይገኝበታል፡፡
«ኮሽ ባለ ቁጥር ተኩስ አይከፈትም» በማለት ምላሻቸውን መስጠት የጀመሩት ኮሚሽነሩ፣ የሕዝብ እሮሮ መኖሩ እውነት ቢሆንም ዕርምጃውን ለመውሰድ ጥናት እንደሚያስፈልግ፣ ይህም ጥናት ረዥም ጊዜ እንደወሰደ ተናግረዋል፡፡
‹‹የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ በጥቃቅን ጉዳዮች ነው ጊዜያችሁን የምታጠፉት፣ ትንንሽ አሳዎችን እንጂ ትልልቅ አሳዎችን አታጠምዱም፤» በሚል ኮሚሽኑን ይወቅሱ እንደነበር ያስታወሱት ኮሚሽነሩ፣ አሁን የተወሰደው ዕርምጃ ተግባራዊ እንዲሆን ጥናትና ምርመራውን ያዘዙት አቶ መለስ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ 
ጥናቱ የተጀመረው አቶ መለስ በሕይወት በነበሩበት ጊዜ ማለትም የዛሬ ዓመት ከአሥር ወር አካባቢ መሆኑን፣ ከአቶ መለስ ሕልፈት በፊት በመጨረሻዎቹ ጊዜያት ጥናቱ ተጠናቆ ለውሳኔ ቀርቦ እንደነበረ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል፡፡
‹‹በጥናት ውጤቱ ላይ ተመሥርቶ ውሳኔ ሳይሰጥ በአቶ መለስ ላይ የጤና ችግር፣ እንዲሁም ሌሎች ጊዜ የሚፈልጉ አስቸኳይ ጉዳዮች ተፈጠሩ፡፡ በኋላም የመንግሥት እንደገና መደራጀትና ሌሎች ነገሮች እንደነበሩ ሁላችንም የምናውቀው ነው፡፡ ከዚያ ተነስቶ ነው ዕርምጃ የተወሰደው፤›› ሲሉ የዘገየበትን ምክንያት አስረድተዋል፡፡ 
በገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ላይ ቅድሚያ ተሰጥቶ ጥናት የተሠራበት ምክንያት፣ በንግድ ኅብረተሰብ ውስጥ የተደላደለ ውድድር እንዳይኖር በኃላፊዎች የሚፈጸሙ የሙስና ወንጀሎች ችግር በመሆናቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ 
የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ በሚነደፍበት ወቅት ትኩረት እንዲደረግባቸው ከተለዩ ተቋማት መካከል በቀዳሚነት የተለየው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
‹‹ግማሹ ግብር ከፋይ ነው ግማሹ ግብር አይከፍልም፡፡ ግማሹ ታክስ ከፍሎ ዕቃ ያስገባል፡፡ ግማሹ ታክስ አይከፍልም፡፡ በዚህ ምክንያት በንግዱ ኅብረተሰብ ውስጥ ሚዛናዊና የተደላደለ ውድድር እንዳይኖር ችግር ፈጥሯል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለልማት የሚውለው ገንዘብ በመንገድ ላይ እየቀረ ነው፤›› በማለት ያብራሩት ኮሚሽነሩ፣ በቅድሚያ በዚህ ላይ ማተኮር ተገቢ መሆኑ ታምኖበት ጥናቱ መከናወኑን ገልጸዋል፡፡
ሌላው ከሕዝብ ተሰብስቦ በቋሚ ኮሚቴው የቀረበው ጥያቄ ዕርምጃው ለምን አሁን ተወሰደ? እንዲሁም አብረው የወሰኑ ሌሎች ባለሥልጣናትና ባለሀብቶች ሊኖሩ ስለሚችሉና ሁሉም ላይ ዕርምጃው አንዴ ባለመወሰዱ መረጃ ሊደብቁ ራሳቸውንም ሊያሸሹ ዕድል አይሰጥም ወይ? የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ዕርምጃ ለመውሰድ ጥናቱ ጊዜ መውሰዱን ገልጸው፣ ከዚህ ውጪ ግን ሌላ ምክንያት እንደሌለ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል፡፡ 

Wednesday, May 15, 2013

ግንቦት 7 - ታሪካዊ ቀን




በግንቦት 7/1997 ምርጫ 524 የምክርቤት ወንበሮች ለምክር ቤት ቀረቡ፡፡ 23 የሚሆኑት በነሐሴ ወር በሱማሌ ክልል ለሚደረገው ምርጫ ወደጎን ተተዉ፡፡

ግንቦት 7 በተካሄደው ምርጫ ተሳትፌያለሁ፡፡ ማን ይናገር የነበረ፤ ማን ያርዳ የቀበረ እንደሚባለው ያየሁትን፣ የሰማሁትን፣ የተሳተፍኩበትን ነው የማቀርበው፡፡ እኔ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ በሦስተኛ ሰው አድርጌ ታሪኩን ላቀርበው ሞክሬ፤ ራቀብኝ፣ ባዕድ ሆነብኝ፣ የኔ መስሎ አልሰማህ አለኝ፡፡ እናም ታሪኩን በቀጥታ ለመተረክ ወሰንኩ፡፡

ግንቦት 7/1997 ከጠዋቱ 12 ሰዓት ከቤቴ ወጥቼ ወደምርጫጣቢያ አመራሁ፡፡ ከምኖርበት ሰፈር ወደምመርጥበት ጣቢያ ለመሄድ ከ15 እስከ 20 ኪ.ሜ. መንዳት ነበረብኝ፡፡ በጠዋት የተነሳሁትም አንድም ቀደም ብዬ ከመረጥኩ በኋላ ከተማውን ተዘዋውሬ ለማየት እንዲረዳኝ በማሰብ ነበር፡፡ ዘጠኝ ኪሜ ያህል ተጉዤ መገናኛ አካባቢ ስደርስ ከአንድ የምርጫ ጣቢያ ፊትለፊት ረዥም ሰልፍ አየሁ፡፡ መኪናዬን ትንሽ ቆም አድርጌ ሰልፉ ምን ያህል ረዥም እደሆነ ለመቃኘት ሞከርኩ፡፡ ሰልፉ እየተጠማዘዘ ቢያንስ 300 ሜትር የሚያክል ቦታ ይዟል፡፡ የተሰለፈውን የሰው ዓይነት ለማየትም ሞከርኩ ዝንቅ ነበር፡፡ ወንድ/ሴት፣ ትልቅ/ትንሽ፣ ወጣት/አዛውንት ሁሉም በትዕግስት ተሰልፈው ይጠብቃሉ፡፡ እንዴት በጥዋት ሊነሱ ቻሉ ብዬ እያሰብኩ መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ መገናኛ አደባባዩጋ ስደርስ ወደሰሜን አቅጣጫ ወደሚወስደው መንገድ ወደቀኝ ታጠፍኩ፡፡ ወደ እንግሊዝ ኤምባሲ ወደሚወስደው መንገድ፣ በድሮው አጠራር ወይዝሮል ወደሚባለው መንገድ ወደሚያስገባው አደባባይ ደርሼ ወደግራ ታጠፍኩ፡፡ ከዚህ ቦታ ጀምሮ ምርጫ የማደርግበት ሰፈር እስከምደርስ ድረስ ስድስት ወይም ሰባት የምርጫ ጣቢያዎች አየሁ፡፡ ሁሉም ቦታዎች እጅግ በጣም በርካታ ሰዎች ተሰልፈው በትዕግስት ይጠባበቃሉ፡፡ እንደዕንቁ ጠብቀው ያቆዩት የምርጫ ካርዳቸውን ከሳጥናቸው ለመጨመር በጉጉት ይጠብቃሉ፡፡

መጀመሪያ እንዳየሁት የምርጫ ጣቢያው ሁሉ ሌሎች ቦታዎችም የተሰለፉት ዓይነት ተመሳሳ ነበር፡፡

Tuesday, May 14, 2013

ሙስናን በስንጥር! ከዚያስ?

inter
 
 
በቀረጥ፣ በሙስናና ባለስልጣናትን የንግድ ሸሪክ በማድረግ ኢትዮጵያን እየጋለቡዋት ያሉ “ባለሃብቶችና አሽከሮቻቸው” እስካልተነኩ ድረስ ኢህአዴግ በሙስና ላይ የጀመረውን ትግል ሙሉ ሊያደርገው እንደማይችል ተገለጸ። ጅማሮው የችግሩ ቁልፍና እምብርት በሆነው ተቋም ላይ መሆኑ የሚደነቅ እንደሆነ የሚገልጹ ክፍሎች ደግሞ ድሩ ያልተበተበው የለምና የመጨረሻው አካሄድ ወዴት እንደሚያመራ ለመገመት ቢቻልም ጅምሩ ይገፋል የሚል ጥርጣሬ እንዳላቸው አስታውቀዋል።
የባለስልጣናት ሚስቶችን፣ ዘመዶችና ወዳጆችን በተቋሞቻቸው ውስጥ በማይመጥኑት ሃላፊነት በመመደብ፣ ከተለያዩ የማማለያ ሽልማቶች ጋር ከፍተኛ ደሞዝ በመክፈል፣ አንዳንዴም ውጪ አገር ድረስ የህክምና ወጪ በመሸፈን ሰበብ የአገሪቱን የአመራር በትር ጨብጠው አገሪቱን እያለቡ ያሉት ወገኖች በይፋ እንደሚታወቁ የሚገልጹ ክፍሎች “አሁን ተጀመረ የተባለውና ይፋ የተደረገው የሙስና ትግል እነዚህን ክፍሎች ብብቱ ስር ይዞ የሚቀጥል ከሆነ ከቀልድ አይዘልም” ሲሉ ጥርጣሬያቸውን ያስቀምጣሉ።
አትራፊ የሆኑ የህዝብና የአገር ተቋማትን ወደ ግላቸው ያለ ክፍያ፣ ያለ ተመጣጣኝ ዋጋ፣ በተጭበረበረ ጨረታና አሰራር ወደ ግላቸው በማዞር አቶ መለስ “ተራው ህዝብ” በማለት በሚጠሩት ህዝብ ትከሻ ላይ እንዳሻቸው የሚዘሉትን “የሙስና አባቶችን” መታገል የማይችል የጸረ ሙስና ቀረርቶ ከተራ የፖለቲካ ልዩነት የዘለለ መነሻና መድረሻ ሊኖረው እንደማይችል እነዚሁ ወገኖች ይናገራሉ።

Ethiopian journalist's last chance for freedom


by Christiane Amanpour and Cynthia McFadden
January 2, 2013 -- A few months ago, we had the honor of hosting the 2012 Courage in Journalism Award for the International Women's Media Foundation. It was a moving, even glittering event. But there was one striking absence. Journalist Reeyot Alemu could not come to New York to receive her award because she is languishing in an Ethiopian prison. On January 8th, an Ethiopian court will decide Alemu’s final appeal. It is her last hope of freedom.

UPDATE: The Court of Cassation at the Ethiopian Federal Supreme Court upheld Alemu's conviction and 5-year sentence on January 8, 2013.

Alemu was arrested last year and thrown into jail for criticizing the Ethiopian government. She was well aware of the risk she was taking. “I was preparing articles that oppose injustice. When I did it, I knew that I would pay the price for my courage and I was ready to accept that price,” she told us.
The price was a 14-year sentence in Ethiopia's notoriously ill-maintained Kaliti prison where prisoners of conscience share quarters with violent criminals. Because she has refused to testify against fellow journalists, Alemu has been put in solitary confinement. All this, simply for writing articles.
After her arrest, Alemu was held without charge or access to legal counsel for three months. Using its controversial 2009 Anti-Terrorism Proclamation, the Ethiopian government accused Alemu of conspiracy to commit terrorist acts and participation in a terrorist organization. What has happened to Alemu is a powerful reminder that the freedom on which we built our careers can still not be taken for granted in other parts of the world.
Feteh (“Justice”), the independent newspaper Alemu wrote for, has since been shut down.
Under Prime Minister Meles Zenawi, who ruled the country for 21 years until his death in August, Ethiopia jailed more journalists than any other country in Africa (except for Eritrea.) For a country which had courageously liberated itself from the yoke of terrifying dictatorship, it is a sad legacy.
Last month, the new Ethiopian Prime Minister, Hailemariam Desalegn, made a move to greater political openness in appointing members of the four main ethnic-based parties to key cabinet positions. It is a good first step.
Whether Desalegn's effort to build a more ethnically diverse cabinet is an honest attempt to democratize the Ethiopian political process or simply a move to consolidate his power will hinge on allowing Ethiopia's independent media to exercise its press freedom without fear of government harassment. The release of imprisoned columnist Reeyot Alemu would be a good start. 
Christiane Amanpour is a news anchor of CNN and ABC News. Cynthia McFadden is a news anchor of ABC News. They serve on the IWMF Board of Directors.

See also:
IWMF interview with Swedish journalist Martin Schibbye
Reeyot Alemu - Imprisoned for defending free speech in Ethiopia - January 4, 2013

Monday, May 13, 2013

የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብቶች በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም (በተለይ ለዞን 9)


Prof. Mesfin Woldemariam በሥራ ላይ አለ የሚባለው በ1987 ዓ.ም. የወጣው ሕገ መንግሥት አንቀጽ 30ና 31 የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት፣ የመደራጀት መብት ይደነግጋሉ፤ ነገር ግን ሁለቱም አንቀጾች ግን እያሉ መፍረሻውን ወይም ማርከሻውን አብረው ይገልጻሉ፤ እንዳያማህ ጥራው እንዳይበላ ግፋው ነው፡ይህ ዘዴ በአጼ ኃይለ ሥላሴም ሆነ በደርግ ሕገ መንግሥቶች ውስጥ የሚታይ ነበር፡፡
የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የመውጣት መብቶች የሕዝቡን ስሜትና ፈቃድ ለማወቅ ለሚፈልግ መንግሥት የእነዚህ መብቶች በተግባር መዋል በጣም ፈላጊ ነው፤ ምክንያቱም መንግሥትንና ሕዝብን ያቀራርባሉ፤ የእነዚህ መብቶች መታፈን የሚያሳየው በመንግሥት ፋንታ አገዛዝ መኖሩንና ሕዝቡን ያለፈቃዱ በኃይል ብቻ የሚገዛ መሆኑን ነው፡፡
አንቀጽ 30‹‹ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነጻነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፤›› ከአለ በኋላ ‹‹ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ ለማስጠበቅ አግባብ ያላቸው ሥርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ፤›› በማለት የአንቀጹን ዋና ርእስ ያደበዝዘዋል፤ ያውም ምንም ትርጉም በሌለው ማመካኛ ነው፤ እግዚአብሔር ያሳያችሁ መሠረታዊ የሆነ የዴሞክራሲ ማሙያዎች የሆኑትን የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍን የማድረግ መብት ‹‹ዴሞክራሲያዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ›› በሚል በተምታታና ግልጽ ባልሆነ አስተሳሰብ ዋናውን መብት ለመገደብ ‹‹ሕጋዊ›› የሚመስል ማመካኛ ፈጠሩ፤ በዚህም ምክንያት በሕገ መንግሥቱ የተደነገጉ የሚመስሉት አንቀጾች በተግባር ታግተዋል፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመሰብሰብም ሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መትረየስንና ክላሽን የሚጋርድና የሚከላከል ጥላ ያስፈልጋል፤ አነዚህ የሕገ መንግሥቱ አንቀጾች ከሥራ ውጭ በመሆናቸው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበርና የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ወደአለመኖር ተሸጋግረዋል፡፡
አሁን ደግሞ በፖሊቲካ ፓርቲዎች ላይ ጭቆናውና አፈናው እየበረታ በመሄዱ ፖሊቲካ ፓርቲዎች ሕዝባዊ ስብሰባ የሚያደርጉበት አዳራሽ (የግልም ሆነ የመንግሥት) ማግኘት የማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፤ በሰላማዊ ሰልፍም አገዛዙ መሳቂያና መሳለቂያ ሆኖአል፤ ለግራዚያኒ በኢጣልያ የሚሠራውን ሐውልት ለመቃወም ጥቂት ዜጎች በስድስት ኪሎ ቢሰበሰቡ ፖሊሶችና የደኅንነት ነጭ ለባሾች እየደበደቡ ይዘው፣ አንድ ቀን አስረው በበነጋታው በዋስ ለቀዋቸዋል፤ በፋሺስት ኢጣልያ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣት ካልተፈቀደ ለምን ይፈቀዳል?በዚህ ሁሉ ላይ ጋዜጠኞችን ሽብርተኞች እያሉ ወደወህኒ ቤት በመወርወር ጋዜጠኞች ሁሉ አንድም ወደስደት አንድም ወደወህኒ እየገቡ ነጻ ጋዜጣ እየጠፋ ነው፤ ስለዚህም በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ሁለገብ አፈና ሰፍኖአል ለማለት ይቻላል፡፡
በኢትዮጵያ ሕዝቡ ቤቱ ሲፈርስ፣ መሬቱን ሲነጠቅ፣ ከኑሮው እየተፈናቀለ ሲባረር፣ ፍትሕ ሲጠፋ፣ ክብሩንና ኩራተን ተገፎ በያገሩ ሲሰደድና ውርደት ሲደርስበት ተሰብስቦ ለመወያየት መብት የለውም፤ በተናጠል እንባውን እያፈሰሰ ወደአምላኩ ማመልከት ልማድ ሆኖአል፤ በአገዛዙ ወንበር ላይ የተቀመጡት እግዚአብሔር የኢትዮጵያን ሕዝብ ግፍ የማያይ፣ ጩኸቱንም የማይሰማ ይመስላቸዋል፤ አግዚአብሔር ግን ሁሉንም ይመዘግባል፤ ለንስሐ የሰጣቸው ጊዜ ሲያበቃ ፍርዱን ለእያንዳንዱ ይሰጣል፤ ያን ጊዜ ኃይልም፣ ሀብትም፣ ሥልጣንም የሕዝብ ይሆናል፡፡

የአቶ ገብረዋህድ ባለቤት በቁጥጥር ስር ዋሉ

የአቶ ገብረዋህድ ባለቤት በቁጥጥር ስር ዋሉ

በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የተያዙት የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ ባለቤት ኮሎኔል 
ሃይማኖት ተስፋይ ባለቤታቸው ከተጠረጠሩት ወንጀል ጋር ተያያዥ የሆኑ ሰነዶችን ሲያሸሹ በመገኘታቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ከፖሊስ ያገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ኮሎኔል ሃይማኖት ከመኖሪያ ቤታቸው ወስደው በሌሎች ግለሰቦች እጅ እንዲደበቁ ያሸሻቸው ሰነዶች በተለያዩ ቦታዎች በአቶ ገብረዋህድ ስም የተመዘገቡ የቤትና የቦታ ካርታዎች ናቸው፡፡
ኮሎኔል ሃይማኖት ካርታዎችን ሲያሸሹ ጥቆማ የደረሳቸው የደህንነትና የፖሊስ ሃይሎችም ክትትል በማድረግ ካርታዎቹን ከተደበቁበት ቦታ ይዘዋቸዋል፡፡
በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ግንቦት 2/ 2005 በቁጥጥር ስር በዋሉት ግለሰቦች ቤት በተደረገው ብርበራ ከፍተኛ መጠን ያለው የኢትዮጵያና የውጭ ሃገራት ገንዘብ እንዲሁም የተለያዩ ሰነዶች መገኘታቸው ይታወሳል፡፡ 

Monday, March 4, 2013

ወያኔ ቅዠት እንጂ ራዕይ የለውም!



በመቅደስ አበራ (ከጀርመን)
ትላንት የተናገሩትን ዛሬ፤ ዛሬ የተናገሩትን ነገ የማይደግሙ ከሀዲ አንባገነን እና ዘረኛ ቡድኖች የስልጣን ኮረቻ በሀይል ከተፈናጠቱበት እለት ጀምሮ የተለያዩ የማወናበጃ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ የበርካታ ንጹሀን ዜጎችን ህይወት ቀጥፈዋል አስቀጥፈዋል፡፡እንኳን እንደጠላት የሚቆጥሩትንና በመርሃ ግብራቸው ነድፈው መጥፋት አለበት ብለው የፈረጁትን ህዝብ ቀርቶ አርነት እናወጣሀለን እያሉ ክእናንተ በመፈጠራችን ኮራንባችሁ የሚሏቸውን የትግራይን ንጹሀን ዜጎች ሳይቀር  የራሳቸውን የስልጣን ዕድሜ ለማራዘም ውድ ህይወታቸውን እንዲገብሩ አድርገዋል፡፡ የሀውዚንን ጭፍጨፋ አቀናብረዋል፣በ1991ዓ.ም በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል በተደረገው  ጦርነት ከ70000 በላይ የጠርነቱ ሰለባ ሁነዋል፡፡አልሻባብን ለመደምስስ በሚል በሶማሊያ በረሃ የረገፉትን ወታደሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡ስልጣን ለወያኔ ከምንም ነገር በላይ ነው፡፡ ስልጣን ከሉአላዊነት፣ከባህር በር ፣ከሀገርና ከህዝብ እንደሚበልጥባቸው ከመጀመሪያው ጀምሮ የወሰዷቸው እርምጃዎች ማሳያ ናቸው፡፡የገንዛ ሀገሩን ቆርሶ ለሱዳን የሚሰጥ፣የባህርበር አያስፈልገኝም የአሰብን ወደብ ውሰዱት፣ኤርትራ እንድትገነጠል ፈቅጃለሁና እውቅና ስጡልኝ እባካችሁ እያለ የአለም መንግትታትን  የተማጸነ፣የገንዛ ዞጎቹን አፈናቅሎ ለውጭ ባለ ሀብቶች መሬታቸውን የሚሰጥ፤የሀገሪቱን ሀብት ለተደራጁ ወንበዴወች የሚያስዘርፍና የሚዘርፍ፤ሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦችን አጥፍቼ  ታላቋን ትግራይን እመሰርታለሁ ብሎ የሚንቀሳቀስ አንባገነን እንዴት ያለ ሀገራዊ ራዕይ ነው የሚኖረው፡፡
ዘረኛው መንግስት በተለያዩ ጊዜያት እንዱን ብሄር በሌላው ብሄር ላይ በማነሳሳት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩት ከመኖሪያቸው ተፈናቅለው ሀብትና ንብረታቸውን ተዘርፈው ለከፍተኛ ችግር ሲዳረጉ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ ለእልፈት ተዳርገዋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎችና ጋዜጠኞችን  በሽብር ስም እያሰረ ንጹሀንን ሲያሸብር ቆይቷል፡፡በርካታ ፓርቲዎች በሰርጎ ገብ ሰላዮች የተነሳ ይዘውት የተነሱትን አላማ እና  የህዝብ አደራ እዳር ሳያደርሱ በጅምር ቀርተዋል፡፡በወያኔ መሰሪ ተንኮል በተቀነባበረ ሴራ ጦርነት ውስጥ ያልገባ ክልልና ብሄር ባይገኝም ውጤቱ እንደሚፈልጉት ስላልሆነላቸው እና የኢትዮጵያ ህዝቦችም ባላቸው አርቆ አስተዋይነትና ረጅም ጊዜ በሰላም አብሮ የመኖር ባህሉ በመታገዝ  የፕሮፖጋንዳቸው ሰለባ ባለመሆናቸው ለወያኔዎች ትልቅ ራስ ምታት ጥሮባቸዋል፡፡እስካሁን ሲጫወትበት የነበረውን ካርድም እንዲቀይርም ተገዷል፡፡ አዲሱ የመጫወቻ ካርድም ከብሄር ግጭት ወደ ሐይማኖታዊ ግጭት ለማሸጋገርም የሚያስችለውን “ጀሀዳዊ ሀረካት”የተሰኘ ዘጋቢ ፊልም በመስራት ከ1500 አመት በላይ አብረው የኖሩትን ሁለቱን ታላላቅ እምነቶች ማለቂያ ወደሌለው ጦረነት በመማገድ የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ቢምክርም እናንተ ከመጣችሁት ገና 21 ዓመታችሁ ነው እኛ ደግም ለረጅም ጊዜ  በፍቅር አብረን ኑረናል፤  የጋራ ጠላታችን ዘረኛው ወያኔ ነው፡፡እኛ ከእነሱ እንሻላለን አንለያይም እያሉ በየአደባባዮ አንገት ላንገት ተቃቅፈው እየተላቀሱ ቁጭታቸውን ሲገልጹ መመልከት የተለመደ ተግባር ነው፡፡ሰሞኑን ለኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕርግራም ሙኒክ ላይ የታየውም ህብረት የዚሁ አካል ነው፡፡
እንዴት እንደ  ኢትዮጵያ ያለች ታላቅ ሀገር እና እንደ ኢትዮጵያውያን ያሉ ቀደምት ህዝቦች እንደ ወያኔ ባሉ ትንሽ ሰዎች ይገዛሉ?እንዴት የአለም ማህበረሰብ በሀሰት የወያኔ ፕሮፖጋንዳ ሲታለል ይኖራል?እስከመቼ ብቻቸውን በምርጫ ተወዳድረው አሸነፍን እያሉ ሲያላግጡ ይኖራሉ? ወያኔዎችስ በቀጣይ ምን የማደናገሪያ ስልት ያመጡ ይሆን? እኔ በበኩሌ በቃ ብያለሁ፡፡ ወያኔ ራዕይ የለውም ኑሮትም አያውቅም፤ ወደፊትም አይኖረውም፡፡የወያኔ  ሀገር እና ህዝብ የማውደም ቅዠት እንጂ ሀገራዊ ራዕይ ብሎ ነገር አያውቅም፡፡በጋራ ጠላታችን ላይ በጋራ እንነሳ!!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/6316

Saturday, March 2, 2013

ተጋዳይ ማትያስ ሹመት ያዳብር

ተጋዳይ ማትያስ ሹመት ያዳብርእንዳይነቀሳቀስ አጁን በስንሰለት ጠፍረህ አሰረኸው፡ሽጉጥክን ደግነህ ተናዘዝ ብትለው፡
በእምነቴ አትምጣ ከፈለክ ያውልህ ደረቴን ለጥይት፡
ደጀ ሰላም ከወራት በፊት አቡነ ማትያስ እንደሚሾሙ ያሳወቀችው እውን ሆኗል፤ከቶ አልበገርም በባዶ ድራማ አድማጭ የለሽ ተረት፡
ሞቴን ከነምነቴ ብሎ በመጽናቱ ግራ የተጋባህ፡
ደንባራ ወያኔ ፊልም መቆራረጥ መቀጣጠል ገባህ፡፡
አንተ አቡ በከር አንድ ጎኔን ሞቀው በጣም አኮራኸኝ ፡
አኩል አልሞቅ አለኝ አንዱ ጎኔ ሳስቶ ክፉኛ በረደኝ ።
እንኳንስ ተከታይ፤ አስተማሪው ካህን መነኩሴው ጳጳሱ፡
ለምነት አለቆም አለ አሳሳችው ነፍሱ።
ኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሆኗ ቀረና የእምነት ማህደር፡
ታጋይ ተፈራርቆ ይሾምባት ጀመር።
የሃይማኖት መሪ በግዜር ይመረጣል ተብይ አድጌ፡
አገር በጾም ጸሎት ትጸናለች ሲባል ተምሬ አድጌ፤
ታጋይ ጳጳስ ሲሆን ስተቱ የማን ነው? መልስ አጣሁ ፈልጌ።
በመርዝ በጥይት ወገኑን ጨርሶ የመጣ ሹመኛ ደብሩን ቢረከበው፡
እግዜር የሾመው ነው በሚል አጉል ባህል መስቀል ልሳለም ነው?
ወይስ
አንት እርኩስ መንፈስ ተጣልቼሃለሁ፡
መስቀልህ ይቅርብኝ ቤቴ ጸልያለሁ፡
ገንዘቤም በኪሴ ለምን ጦርሃለሁ፡
ብዬ ላሳርፈው?
ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን የምትሆነው ፈሪሃ እግዚአብሄር ያለው የሃይማኖት መሪ ሲኖራት እንጂ የፖለቲካ ስልጣን በተቆጣጠሩ ባለስልጣናት የሚሾም ካድሬ ቁጥጥር ስር ሆና አደለም ፡ ስለዚህ ለተዋህዶ ሃይማኖት ተከታዮች ሁሉ ማስተላለፍ የምፈልገው ምልእክት፡ ስርዓት እሰኪከበር ድረስ ጸሎታችሁን በቤታችሁ ገንዘባችሁን በኪሳችሁ እንድታረጉት እንዲሆን ነው፡ በገዛ ገንዘባችሁ ወያኔን የምታዳብሩበት ምክንያት አይኖርም፡፡
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ
እስከ ነጻነት