Friday, October 25, 2013

በእስር ላይ ያሉ የሙያ ኣጋሮቹ ሳይፈቱ እሱ እንዴት ወደ እስር ማገዶው ደፈረ?


ጉድ በል ...ኣለ ኣሉ ፤ ገና ብዙ እንሰማለን። (ከታዘብኩት)

እስኪ ይታያችሁ በአሁን ሰኣት እየተባባሰ  በመጣው ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው የሰባዊ መብት እረገጣ፤ እስራት እና የነጻ ሚዲያ አፈና ፤ እስር ቤት ውስጥ ታጉረው ያለፍትሕ በሃሰት ክስ ተመስርቶባቸው በስቃይ ላይ የሚገኙ ብዙሃን ጋዜጠኞች ባሉባት ኢትዮጲያ ፤ያውራምባ ታይምስ ድህረ ገጽ ዋና አዘጋጂ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሁለት አመት በፊት መንግስት በሚፍጽመው ህገወጥ ተግባር እና ኢ ሰብአዊ ድርጊት ነቅፌና ተቃውሜ በመጻፌ በመንግስት እንደ ህገ ወጥ በመቆጠሬ፤በመወንጀሌ እና ለእስር በመፈለጌ ከሃገሬ ተሰደድኩ የሚለው ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ኣሁን ደሞ ከሁለት አመት በሁዋላ ሊያስረው ይፈልገው ወደነበረው መንግስት በራሱ ኣንደበት፤ባደባባይ ልመለስ ነው ይለናል። ለምን ሲባል ስራየን በጥራት እና በብቃት ለመስራት አዛው ቦታው ምንጩጋ መሆን እንዳለበት ኣሁን ስለተገለጠልኝ ነው ይለናል። 
እንዲያው በዛው ሌላውንም ስምምነት በተመለከተ ጠቆም አርጎን ቢያልፍ ጥሩ ነበር አንጂ አለበለዛማ ወያኔ ያሳደደውን መጣሁልህ ሲባል አበባ ይዞ ዌል ካም ሲል ኣይተንም ሰምተንም ኣናውቅ።
ወይ ከዜሮ ዜሮ አቤት የቅንድቡ ማማር ካላለ፤ አለበለዛ አንደ ፱፯ቱ ምርጫ በሙስና ካልትጭበረበረ፥ ወይንም ደግሞ "አንደር ከቨር ሚሽን አኮምፕሊሽድ"  ካላለን እኮ እንዴት ተደርጎ?  እንዴት እንቀበል?  

መለካት ያለብኝ በምሰራው ስራ መሆን ነው ያለበት የሚለን ጋዜጠኛ ዳዊት ደጋግሞ የሚናገራቸው  በእስር ላይ ያሉ የሙያ ኣጋሮቹ ከእስር ሳይፈቱ ፤ እሱ እንዴት ወደ እስር ማገዶው ሔጀ በሰላም እሰራለሁ ብሎ ደፈረ? ምንስ ማረጋገጫ ቢኖረው ነው።  CPJ (Committee to Protect  Journalists) የሚባለዉ ስለ ነጻ ሚዲያ እና ስለ ጋዜጠኞች መብት ተሙዋጋች ድርጂት በሰፊዉ እንደሚዘግበዉ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የነጻ ፕሬስ ጋዜጠኛ ሆኖ መገኘት እንደ ወንጀል በሚቆጠርበት ወቅት አና አስር አና አፈና የተባባሰ በሆነብት ጊዜ ላይ የመጉዋዝ ሞራሉስ ከየት መጣ? ይህ እንግዲህ ቀስ እያለ የሚገለጥ እውነታ ነው።  

እስኪ ያረገውን ቃለ ምልልስ አንስማ ...




Is his mission accomplished ?

Awramba Times Editor is going back home